የኢትዮጵያ ማዕከላዊነት የሁላችን መሻት ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

Date:

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሆሳዕና ከተማ እየተከበረ በሚገኘው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ላይ ንግግር አድርገዋል።

ለመላው ኢትዮጵያውያን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ የዛሬውን በዓል ያዘጋጀው እና ኢትዮጵያን ያሰባሰበውን ሀዲያን አመስግነዋል።

ኢትዮጵያ አንዱ ከፍ ሌላው ዝቅ የሚልባት ሳይሆን ሁላችን የምንደምቅባት ነች ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

ኢትዮጵያ በሁሉም መመዘኛ ወደ ብርሃን አየተሸጋገረች ባለችበት ወቅት እንዲህ መሰባሰባችን ታሪካዊ ነው ያሉት ጠቅላይ ማኒስትሩ፤ ብርሃኑን ለማጉላት በኅብረት መቆም አለብን ብለዋል።

ኢትዮጵያን ችግሯን ብቻ ሳሆን አቅሟን ማየት እንሚገባ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ ልጆቿ በጠንካራ አንድነት በጋራ ከቆሙ ከፍታዋን ማረጋገጥ ይቻላል ነው ያሉት።

እንደ ድር አብረን ለነገ ትውልድ የምትመች ኢትዮጵያን በጋራ እንሥራ በማለትም ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ የጀመረችውን አስደናቂ ጉዞ ለማስተጓጐል እንቅልፍ የሚያጡ ቢኖሩም ኢትዮጵያን ከጉዞዋ አያቆሟትም ብለዋል።

የኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ ልጆች አንሸማቀቅም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ ተምሳሌት ሆና ትቀጥላለች ሲሉ ተናግረዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...