የአርሰናል የዘንድሮው የሜዳው አለመሸነፍ ግርማ በታሪካዊ ባላንጣው ማንቸስተር ዩናይትድ ተገትቷል። መድፈኞቹ በገዛ ሜዳቸው 2 ለ 3 በሆነ ውጤት ተሸንፈዋል።
📌 የጨዋታው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ታሪካዊ ድል፡ ማንቸስተር ዩናይትድ ከ2017 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በኤምሬትስ ስታዲየም የሊግ ድል ተቀናጅቷል።
የኩንሃ አስደናቂ ጎል፡ማቲየስ ኩንሃ በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ ያስቆጠራት ድንቅ ጎል ለቀያይ ሰይጣኖቹ 3 ነጥብ አስገኝታለች።
የመሪነቱ ግፊት፡ አርሰናል ከአንድ ሳምንት በፊት የ9 ነጥብ ልዩነት ለመፍጠር ዕድል የነበረው ቢሆንም፣ አሁን ግን በሊጉ አናት ላይ ከማን.ሲቲ እና አስቶን ቪላ ያለው ልዩነት ወደ 4 ነጥብ ዝቅ ብሏል።
ወደ ቶፕ 4፡ ዩናይትድ ይህን ድል ተከትሎ ደረጃውን ወደ 4ኛ ከፍ ማድረግ ችሏል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በኤምሬትስ ስታዲየም ያሳየው ብቃት እጅግ የሚደነቅ ነበር። ጨዋታውን በጥልቀት ስንመለከተው ግን የአርሰናል ድክመት ለዩናይትድ ድል ትልቅ መንገድ ከፍቷል።
📝 የጨዋታው ቁልፍ ትዝታዎች፦
የፈጠራ ችግር፦ አርሰናሎች በመጀመሪያው ጎል መሪ መሆን ቢችሉም፣ ዩናይትድ መጫወቻ ቀዳዳዎችን በዘጋባቸው ወቅት ግን ብልሃትና በራስ መተማመን ሲጎድላቸው ታይተዋል።
የዙቢሜንዲ ስህተት፦ መድፈኞቹ መሪ በነበሩበት ወቅት ማርቲን ዙቢሜንዲ የፈጸመው የቸልተኝነት ስህተት ዩናይትድ አቻ እንዲሆን ዕድል ሰጥቷል። ይህ ስህተት የቡድኑን መዘናጋት ማሳያ ነበር።
ድንቅ ጎሎች፦ የዩናይትድን ድል ያረጋገጡት የዶርጉ እና የኩንሃ ድንቅ ጎሎች በኤምሬትስ ላይ ለዩናይትድ ደጋፊዎች ታላቅ ምሽትን ፈጥረዋል።
