የኤርትራዉ ቃል አቀባይ የማነ ገብረመስቀል ምን አሉ?

Date:

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገብረመስቀል፣ መቀመጫውን ዋሽንግተን ያደረገው “ዘ ሴንትሪ” የተሠኘው መንግሥታዊ ያልኾነ ተቋም በኤርትራ ላይ ያወጣው ሪፖርት “የስም ማጥፋት ውንጀላ” ነው በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሠፈሩት ጽሁፍ ውድቅ አድርገዋል።

የማነ፣ የተወሰኑ የተቋሙ የቦርድ አባላት፣ “በአደራዳሪነት ሽፋን የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጦርነትን በማባባስ” የሚታወቁ፣ ለኢትዮጵያ መንግሥት ወግነው የነበሩና የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ ማዕቀብ እንዲጥል ከፍተኛ ሚና የተጫወቱ ነበሩ በማለት ወቅሰዋል።

ተቋሙ “ሥልጣና እ ዝርፊያ፤ የኤርትራ ጦር ጣልቃ ገብነት በትግራይ‘’ በሚል ርዕስ ከቀናት በፊት ባወጣው ሪፖርት፣ ኤርትራ ሠራዊቷን እንደገና እያስታጠቀችና ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦቿም በትግራይ በሰዎች ዝውውር፣ በሰዎች እገታና በሕገወጥ የወርቅ ማዕድን ንግድ እንደሚሳተፉ ገልጦ ነበር። [ዋዜማ]

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...