የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ፣ ኢራንን ስምምነቱን በቀጥታ በመጣስ ከሰዋል፡፡
በቴህራን እምብርት ውስጥ በሚገኙ የመንግስት ኢላማዎች ላይ ከፍተኛ ጥቃቶችን በመፈጸም ብርቱ አጸፋ እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
ውጥረቱ የተፈጠረው እስራኤል ከኢራን የተወነጨፉ ሚሳኤሎችን መለየቷን ካስታወቀች ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ነው።
የቴህራን የመንግስት ቴሌቪዥን ምንም አይነት ሚሳኤል አለመወንጨፉን ሲል አስተባብሏል፡፡
ይህ የተኩስ አቁሙ መፍረስ ዜና የተሰማውየአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ፣ በሀገራቱ መካከል የተኩስ አቁም መደረጉን ካስታወቁ ከሁለት ሰዓታት በኋላ ነው፡፡
