የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰሯቸው ጥናት እና ምርምር ውጤቶች

Date:

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚሰሯቸው የጥናት እና ምርምር ውጤቶች ፖሊሲ አውጭዎች እና ለሌሎችም አካላት እንደ ግብዓትነት እየተጠቀሙት መሆኑ እየተሰማ ነው፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ከዚህ ቀደም ይሰሩ የነበሩ የምርምር ውጤቶች የማህበረሰቡ ችግር ላይ ትኩረት ያላደረጉ ነበሩ፤ ይህም ቢሆን በተወሰነ መልኩ እየተስተካከለ ነው ተብሏል፡፡

ይህ የተባለው ቅድስት ማርያም ዩኒቨርስቲ 23ተኛውን የአፍሪካ የግል ከፍተኛ ትምህርት ዓለም አቀፍ ጉባኤ ባካሄደበት ወቅት ነው፡፡

ዩኒቨርሲቲውም ከዚህ ቀደም የሚሰሩ ጥናት እና ምርምሮች ችግር ሲፈቱ እና የሚመለከታቸው ሲጠቀሙባቸው ማየት የተለመደ አልነበረም አሁን ግን ችግሩ እየቀነሰ መጥቷል ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ያሉ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎቹን አስተምሮ ከማስመረቅ ባለፈ ምን ያህሉ ተማሪ ወደ ስራ ገብቷል፣ ምን ያህሉ የመውጫ ፈተና ውጤት አምጥቷል? እና በሌሎች መስፈርቶች ይመዘናሉ ያሉት የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጦሽኔ ከዛም ባለፈ የትምህርት ተቋማቱ ምን ያህል የምርምር ውጤቶችን ከውነዋል የሚለውን ሳይሆን ምን ያህሉ ጥናት ችግር ፈች ሆነ የሚለውን መመዘን ጀምረናል ብለዋል፡፡

በዚህም መሰረት በአመቱ መጨረሻ ተቋማቱ የሰሯቸው የምርምር ውጤቶች ምን ያህል ችግር ፈች ሆኑ ብለን የምዘና ሂደት እናከናውናለን ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ይህ አሰራርም የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ ተጀምሯል ብለዋል፡፡

ባለፉት አምስት አመታትም በኢትዮጵያ የሚታተሙ የምርምር ውጤቶች በእጥፍ ጨምሯል የተባለ ሲሆን አብዛኞቹም የሚሰሩት በመንግስት የትምህርት ተቋማት ነው ተብሏል፡፡

ከሸገር 102.1

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ክፍሌ አቦቸር እና ‹‹ይህ ነው ምኞቴ…››

ሠሎሞን ለማ ገመቹ ግዮን መጽሔት :- ሻለቃ ከፍሌ አቦቸር...

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...