የካሜሮን ቴሌኮሙኒኬሽን በኢትዮ ቴሌኮም ጉብኝት አደረጉ

Date:

በካሜሩን ቴሌኮሙኒኬሽን (ካምቴል) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጁዲት ያህ ሰንደይ የተመራ የልዑካን ቡድን፣ በዲጂታል ፋይናንሻል አገልግሎት እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ረገድ ተሞክሮዎችን ለመቅሰም የሚያስችል ጉብኝት በኢትዮ ቴሌኮም አደረገ።

ዋና ሥራ አስፈፃሚያችን ፍሬሕይወት ታምሩ የኢትዮ ቴሌኮምን ፈጣን የለውጥ ጉዞ፣ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂ እንዲሁም ከመደበኛ ኮኔክቲቪቲ አገልግሎት ባሻገር በዲጂታል ሶሉሽኖችን የዜጎች፣ ቢዝነስ እና ተቋማትን አቅም በመገንባት የሀገሪቱን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን በማፋጠን ላይ ያለውን ቁልፍ ሚና ገልጸዋል፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባላት በኤክስፒሪያንስ ማዕከላችንና ዳታ ሴንተር ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን፣ በጉብኝቱም ወቅት ከግብርና፣ ከትምህርት፣ ከጤና አጠባበቅ፣ ከማዕድን እና ከስማርት ቱሪዝም ጋር ስለተያያዙ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡

የልዑካን ቡድኑ አባላትም ሶሉሽኖቹ ጠንካራ የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት እየተከናወነ ስለሚገኘው ቁርጠኛ ሥራ ማሳያ ስለመሆናቸው እንዲሁም በኩባንያችን ደንበኞች ቁጥር እድገት ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡

የካምቴል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኩባንያው ቴሌብርን እና ዲጂታል ሥነ-ምህዳርን ለማሳደግ እያደረገ የሚገኘው ጥረት በመላ አፍሪካ የዲጂታል ፈጠራ ፋናወጊ ለመሆን ያለውን አቅም ያሳያል ብለዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...