የኬኒያ እዉቁ የማህበረሰብ አንቂ  በሽብርተኝነት መያዙ ተገለጸ

Date:

ኬኒያዊዉ አክቲቪስት ቦኒፌስ ምዋንጊ፤ አንድ ወር ለሚጠጋ ጊዜ በኬኒያ መንግስትን ተቃዉመዉ ሰልፍ የወጡትን ዜጎች አነሳስቷል በሚል በሽብርተኝነት መያዙ ተገልጿል፡፡

በዚህ የተቃዉሞ ሰልፍ 19 ሰዎች ህይወታቸዉን ማጣታቸዉ ይታወሳል፡፡

‹‹በኢኮኖሚ ችግርና በመንግስት ተጠያቂነት እጦት የተነሳ ተፈጠረ››በተባለዉ የተቃዉሞ ሰልፍ ላይ የሽብር ተግባራትን አመቻችቷል በማለት ነዉ ፖሊስ አክቲቪስቱን መክሰሱን የገለጸዉ፡፡

የከተማዋ ፖሊስ በተቃዉሞ ወቅት በጥቅም ላይ ያልዋሉ የአስለቃሽ ጭስና የጦር መሳሪያዎችን ሰልፈኞቹን አስታጥቆም ነበር ብሏል፡፡

የህግ ምሁራን ምዋንጊ ከሽብርተኝነት በተጨማሪ፤ ህገ-ወጥ ጥይቶችን በመያዝ ጭምር ክስ ሊመሰረትበት እንደሚችል ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም ፖሊስ እንደ ላፕቶፕ፣ስልክና ማስታወሻ ደብተር ከቢሮዉ እና ከመኖሪያ ቤቱ  መዉረሱን አስታዉቋል፡፡

ብዙዎች ክሱ በመንግስት ላይ የሚደረግ ትችትን ለመግታትና የኬንያ ከፍተኛ ተቺዎችን ዝም ለማሰኘት የሚደረግ ሙከራ ነዉ ብለዋል።

ምዋንጊ በኬኒያ ዉስጥ  የረዥም ጊዜ ታጋይና የሲቪል ማህበረሰብ አንቂ ሲሆን፤  ከዚህ በፊት ሙስናን በመቃወም ይታወቃል፡፡

በተጨማሪም የፖሊስ አባላት በሚያደርሱት ጭካኔያዊ ተግባር እንዲሁም ባለስልጣናት በሚፈጽሙት የህግ ጥሰት የተነሳ ተጠያቂ የሚያደርጋቸዉ የለም በሚለዉ አቋሙ ለዛቻዎች፤ ማስፈራሪያዎችና እስሮች መዳረጉን የአፍሪካ ኒዉስ ዘገባ ያመላክታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...