የኮሪያ ኤክስፖርት ኢምፖርት ባንክ (Korea EXIM Bank) በትራንስፖርት፣ በኢነርጂ፣ በጤና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ላይ ለሚከናወኑ 11 የኢትዮጵያ የልማት ፕሮጀክቶች 871 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ድጋፍ ማድረጉ ተገለጸ።
በአጠቃላይ በዚሁ የልማት ትብብር ስምምነት ኢትዮጵያና ደቡብ ኮሪያ 954.2 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚገመት ስምምነት ማድረጋቸው ይታወቃል።ከዚህ ውስጥ 183.2 ሚሊዮን ዶላሩ በኮሪያ አለም አቀፍ ትብብር ኤጀንሲ (KOICA) የሚደገፉ ፕሮጀክቶች ናቸው።
ሁለቱ ሀገራት በቀጣይም በትብብር እንደሚሰሩ የገለጹ ሲሆን ይህ የገንዘብ ድጋፍ በኢትዮጵያ የልማት እንቅስቃሴ ላይ ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይጠበቃል።
