3ኛው የአዲስ አበባ ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2018 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫን አቅርበዋል።
ከንቲባዋ ገቢና ወጪን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ በ2017 በጀት ዓመት ከ233 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ መቻሉን አስታውቀዋል።
የተሰበሰበው ገቢም ከ2016 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ83.3 ቢሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ገልጸዋል።
በገቢ አሰባሰብ ሂደቱ የሌብነትና ብልሹ አሰራር በፈጸመው 247 ሰራተኞች ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም ተናግረዋል፡፡
ባለፉት 11 ወራት የግብይትና የታክስ ህጎችን በላከበሩ እና ደረሰኝ ባልሰጡ 11 ሺህ 283 ነጋዴዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰዱንም አመላክተዋል።
