በዶሃ በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ ውድድር በሴቶች 3ሺ ሜትር መሰናክል አትሌት ሲምቦ አለማየሁ ሶስተኛ ወጥታለች ።
አትሌት ሲምቦ እርቀቱን ለማጠናቀቅ 9:09.27 ወስዶባታል።
አትሌት ሲምቦ በፔሩ ሊማ በተካሄደው የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ መሆኗ የሚታወስ ነው።
በውድድሩ የተካፈለችው አትሌት ሎሚ ሙለታ 8ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች ።
በሴቶች 1500 ሜትር ውድድር አትሌት ሳሮን በርሀ 4ኛ ወጥታለች።
በወንዶች 5ሺ ሜትር አትሌት ሳሙኤል ተፈራ በ13:18.63 በመግባት 4ኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቋል ።
