ጋዜጠኞችን ለቀናት ሰውረው ያቆዩ አካላት ወደ ሕግ ይቅረቡ

Date:

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር ጋዜጠኞችን ያሉበት በማይታወቅበት ሁኔታ ከ10 ቀናት በላይ ሰውረው ያቆዩ አካላት በግልፅ እንዲታወቁ እና በሕግ ፊት እንዲቀርቡ ጠየቀ።

ማህበሩ በአሀዱ ኤፍ ኤም 94.3 FM ሬዲዮ የቅዳሜ ገበያ ፕሮግራም አዘጋጅ  ጋዜጠኛ አብዱሰመድ ከ12 ቀናት በኋላ፤ የሪፖርተር ጋዜጣ ከፍተኛ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ዮናስ ደግሞ ከ10 ቀናት ስወራ ነጻ ወጥተው ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን ማረጋገጡን በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ላይ ባሰፈረው ጽሑፉ አስታውቋል።

ጋዜጠኞቹ ያሉበት በማይታወቅበት ሁኔታ ከ10 ቀን በላይ ተሰውረው መቆየታቸው “ሕገ ወጥ ተግባር ነው” ያለው ማኅበሩ፤ የድርጊቱ ፈጻሚዎች በግልፅ ታውቀው በሕግ ፊት ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርቧል።

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር ይህን ያስታወቀው የሪፖርተር ጋዜጣ ከፍተኛ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ዮናስ አማረ እና በአሀዱ ኤፍ ኤም 94.3 FM ሬዲዮ የቅዳሜ ገበያ ፕሮግራም አዘጋጅ ጋዜጠኛ አብዱል ሰመድ መሀመድ እንደተለቀቁ መገለጹን ተከትሎ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሴቶችን በቤት ውስጥ በማገዝ  መልካም ማህበረሰብ መፍጠር ተጀምሯል

በቤት ውስጥ የሚሠሩ ተግባራትን ተከፋፍሎ በመሥራት ሴቶችና እናቶችን መደገፍ...

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...