ፓላስ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫን አነሳ

Date:

በኮሚኒቲ ሺልድ ዋንጫ ክርስታል ፓላስ ሊቨርፑልን በመለያ ምት አሸንፏል፡፡ በዌይምብሌ በተደረገው ጨዋታ ሁለቱ ቡድኖች መደበኛ 90 ደቂቃውን ሁለት አቻ አጠናቀዋል፡፡


የሊቨርፑልን ሁለት ግቦች አዲስ ፈራሚዎቹ ሁጎ ኢኪቲኬ እና ጀርሚ ፍር,ሪምፖንግ አስቆጥረዋል፡፡ ጃን ፍሊፕ ማቴታ በፍጹም ቅጣት ምት እና ኢስማኤል ሳር በጨዋታ የክርስታል ፓስን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡


አሸናፊውን ለመለየት በተሰጠው መለያ ምት ክርስታል ፓላስ 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡ ሙሀመድ ሳላ እና አሌክሲስ ማክ አሊስተር የሊቨርፑልን ሁለት ተከታታይ መለያ ምትቾች መጠቀም አልቻሉም፡፡


አሰልጣኘ አርን ስሎት በዌይምብሌ ባደረጓቸው ሁለት የፍጻሜ ጨዋታዎች በሁለቱም ለመሸነፍ ተገደዋል፡፡ አሰልጣኝ ኦሊቨር ግላስነር በፓለስ ቤት 2ኛ ዋንጫቸውን አንስተዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...