ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ከኢትዮጵያ ፕሮፌሽናል ተጫዋቾች ማኅበር አመራሮች ጋር ተወያዩ

Date:

በኢ/እ/ፌ ዋና መሥሪያ ቤት የተካሄደው ውይይት የፌዴሬሽኑ እና ማኅበሩን ግንኙነት በማጠንከር የኢትዮጵያ እግር ኳስ እድገትን በሚደግፉበት፣ በእግር ኳሱ የሚከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት ብሔራዊ የውዝግብ መፍቻ ተቋምን ማቋቋም በሚቻልበት፣ ማኅበሩ መልካም ተሞክሮዎችን ከሌሎች ሀገራት ተቋማት የሚቀስምበትን ሂደት በማመቻቸት እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር። በውይይቱ በእግር ኳሱ እያጋጠሙ ያሉ ፈተናዎች በተለይም የተጫዋቾች መብት እና ክለቦች ተጫዋቾችን የሚይዙበት መንገድ ዙርያ ውይይት ተደርጓል።

ክቡር ፕሬዝዳንቱ ተጫዋቾች ለስፖርቱ ዋነኛ እሴት መሆናቸውን ጠቁመው ማኅበሩ የአባላቶቹን አቅም በማሳደግ ዙርያ ጠንክሮ ሊሰራ እንደሚገባ ተናግረዋል።

የሁለቱ አካላት ውይይት እግር ኳሱ ወደተሻለ ምዕራፍ እንዲሸጋገር በቅርበት ለመስራት የጋራ ቁርጠኝነት በመግባት ተጠናቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...