” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትየዚምባብዌ መንግሥት ከአሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ያለ ታሪፍ እንዲገቡ ወሰነ

Date:

👉 በአዲስ አበባና ጎንደር ከተሞች አንዳንድ አካባቢዎች ላይ በቅድመ ጥገና ሥራ ምክንያት ዛሬ ኃይል ተቋርጧል

ሲስተም ላይ ባጋጠም ብልሽት ምክንያት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎች እንዲሁም የዲጂታል የክፍያ አማራጮችን ጨምሮ ከኢንተርኔት አገልግሎት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የድህረ ክፍያ አገልግሎቶች አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።

ችግሩ ተፈትቶ የተቋረጠው አገልግሎት እስከሚመለስ ድረስ ደንበኞች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ዲስትሪክቶች ወይም አገልግሎት መስጫ ማዕከሎች በአካል ወይም በቀጥታ ስልክ በመደወል ተገቢውን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል፡፡

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዛሬ መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በሚያከናውነው የቅድመ ጥገና ሥራ ምክንያት፤ በአዲስ አበባና ጎንደር ከተሞች አንዳንድ አካባቢዎች ላይ በዕቅድ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ አስታውቋል፡፡

በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ከጠዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 9:30 እንዲሁም፤ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18፣ ሻዋ ዳቦ፣ ኮሌጅ፣ ባህር ሰላም እና አካባቢዎቻቸው ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ድረስ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ግዮን መጽሔት ዛሬ ቅዳሜ ግንቦት 1 2018 ዓ.ም ገበያ ላይ ውሏል !!!

በኢትዮጵያ ነፃ ኘሬስ ከ25 ዓመት በላይአገልግለናል !!! -የአርበኞች አደራና የትውልዱ...

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...