” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትየዚምባብዌ መንግሥት ከአሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ያለ ታሪፍ እንዲገቡ ወሰነ

Date:

👉 በአዲስ አበባና ጎንደር ከተሞች አንዳንድ አካባቢዎች ላይ በቅድመ ጥገና ሥራ ምክንያት ዛሬ ኃይል ተቋርጧል

ሲስተም ላይ ባጋጠም ብልሽት ምክንያት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎች እንዲሁም የዲጂታል የክፍያ አማራጮችን ጨምሮ ከኢንተርኔት አገልግሎት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የድህረ ክፍያ አገልግሎቶች አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል።

ችግሩ ተፈትቶ የተቋረጠው አገልግሎት እስከሚመለስ ድረስ ደንበኞች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ዲስትሪክቶች ወይም አገልግሎት መስጫ ማዕከሎች በአካል ወይም በቀጥታ ስልክ በመደወል ተገቢውን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል፡፡

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዛሬ መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም በሚያከናውነው የቅድመ ጥገና ሥራ ምክንያት፤ በአዲስ አበባና ጎንደር ከተሞች አንዳንድ አካባቢዎች ላይ በዕቅድ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ አስታውቋል፡፡

በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ከጠዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 9:30 እንዲሁም፤ በጎንደር ከተማ ቀበሌ 18፣ ሻዋ ዳቦ፣ ኮሌጅ፣ ባህር ሰላም እና አካባቢዎቻቸው ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 10፡00 ድረስ የኃይል አቅርቦት እንደሚቋረጥ ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...