19ኛዋ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች መርከብ ጅቡቲ ደረሰች

Date:

ኤምቪ አባይ ሁለት የተባለችው የኢትዮጵያ መርከብ ለ2017/18 የምርት ዘመን ግብዓት የሚሆን 55 ሺህ ሜትሪክ ቶን ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ በጅቡቲ ወደብ ማራገፍ መጀመሯን የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን አስታውቋል።

ለ2017/18 የምርት ዘመን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ከተቃደው 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እሰከ መጋቢት 21 ድረስ 11 ሚልየን ኩንታል የሚጠጋ የአፈር ማዳበሪያ በ19 መርከቦች ተጭኖ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡

ከዚህ ውስጥ ከ900 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የሚሆነው የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ እንደተጓጓዘ እና 118 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ደግሞ በጅቡቲ ወደብ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

በ19 መርከቦች ከተጫነው ውስጥ 682 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ዳፕ እንዲሁም ከ336 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ዩሪያ የተሰኘው የአፈር ማዳበሪያ እንደሆነ ከመሥሪያ ቤቱ የተገኘው መርጃ ያሳያል፡፡

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የጣሊያን የመከላከያ ስምምነቶችና የፖለቲካዊ ድጋፎች

በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣውን የጸጥታ ስጋት ተከትሎ፣ ጣሊያን ለባህረ...

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ”ንዋይ” የተሰኘ መተግበሪያን ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ዜጎች...

የነዳጅ እጥረት አሽከርካሪዎችን ለከፋ እንግልት እየዳረገ ነው

በአዲስ አበባ እና በልዩ ልዩ የክልል ከተሞች የሚስተዋለው የነዳጅ...

ሼክ ኢብራሂም ቱፋ በኢራን ኤምባሲ በመገኘት ሀዘናቸውን ገለጹ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼክ ኢብራሂም...