19ኛዋ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች መርከብ ጅቡቲ ደረሰች

Date:

ኤምቪ አባይ ሁለት የተባለችው የኢትዮጵያ መርከብ ለ2017/18 የምርት ዘመን ግብዓት የሚሆን 55 ሺህ ሜትሪክ ቶን ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ በጅቡቲ ወደብ ማራገፍ መጀመሯን የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን አስታውቋል።

ለ2017/18 የምርት ዘመን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ከተቃደው 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እሰከ መጋቢት 21 ድረስ 11 ሚልየን ኩንታል የሚጠጋ የአፈር ማዳበሪያ በ19 መርከቦች ተጭኖ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡

ከዚህ ውስጥ ከ900 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የሚሆነው የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ እንደተጓጓዘ እና 118 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ደግሞ በጅቡቲ ወደብ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

በ19 መርከቦች ከተጫነው ውስጥ 682 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ዳፕ እንዲሁም ከ336 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ዩሪያ የተሰኘው የአፈር ማዳበሪያ እንደሆነ ከመሥሪያ ቤቱ የተገኘው መርጃ ያሳያል፡፡

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...