19ኛዋ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች መርከብ ጅቡቲ ደረሰች

Date:

ኤምቪ አባይ ሁለት የተባለችው የኢትዮጵያ መርከብ ለ2017/18 የምርት ዘመን ግብዓት የሚሆን 55 ሺህ ሜትሪክ ቶን ዳፕ የአፈር ማዳበሪያ በጅቡቲ ወደብ ማራገፍ መጀመሯን የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን አስታውቋል።

ለ2017/18 የምርት ዘመን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት ከተቃደው 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ እሰከ መጋቢት 21 ድረስ 11 ሚልየን ኩንታል የሚጠጋ የአፈር ማዳበሪያ በ19 መርከቦች ተጭኖ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ ጨምሮ ገልጿል፡፡

ከዚህ ውስጥ ከ900 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ የሚሆነው የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ እንደተጓጓዘ እና 118 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ደግሞ በጅቡቲ ወደብ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

በ19 መርከቦች ከተጫነው ውስጥ 682 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ዳፕ እንዲሁም ከ336 ሺህ ሜትሪክ ቶን በላይ ዩሪያ የተሰኘው የአፈር ማዳበሪያ እንደሆነ ከመሥሪያ ቤቱ የተገኘው መርጃ ያሳያል፡፡

@sputnik_ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...