በህገ-ወጥ መንገድ የተከማቸ 200 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በቁጥጥር ስር ዋለ
በደብረ ማርቆስ ከተማ በህገ-ወጥ መንገድ የተከማቸ የአፈር ማዳበሪያ በቁጥጥር ስር ማዋል መቻሉን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ገልጿል፡፡
ከማህበረሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት በአብማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 9 አባብዙነህ ጉርድ በግለሰብ ቤት የተከማቸ 200 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ መገኘቱን የገለፁት የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ቢምረው አሰፍ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ አስፈላጊውን ክትትል እያደረገ ይገኛል ተብሏል።
