232 መንገደኞችን አሳፍሮ ወደለንደን ያመራ የነበረ የኤር ኢንዲያ ንብረት የሆነው ቦይንግ 787 ድሪም ላይነር አውሮፕላን ከተነሳ በኋላ መከስከሱ ተሰማ።
አውሮፕላኑ ከአህመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ በተነሳበት ቅፅበት መከስከሱን ቢቢሲ አስነብቧል።
በወቅቱ 12 የአውሮፕላኑን ሰራተኞች ጨምሮ 232 መንገደኞችን አሳፍሮ የነበረ ሲሆን፥ ከተነሳ በኋላ በ190 ሜትር ከፍታ ላይ ከአየር በረራ ተቆጣጣሪዎች ጋር የመጨረሻ ግንኙነት አድርጓል ተብሏል።
የአደጋው መንስኤ እስካሁን ያልተገለጸ ሲሆን፥ አውሮፕላኑ በመኖሪያ መንደር አካባቢ መከስከሱንም ነው ዘገባው ያመላከተው።
በህይወት ሰው ስለመትረፉ ምንም የተባለ ነገር የለም።
