232 መንገደኞችን አሳፍሮ የነበረ አውሮፕላን በህንድ ተከሰከሰ

Date:

232 መንገደኞችን አሳፍሮ ወደለንደን ያመራ የነበረ የኤር ኢንዲያ ንብረት የሆነው ቦይንግ 787 ድሪም ላይነር አውሮፕላን ከተነሳ በኋላ መከስከሱ ተሰማ።

አውሮፕላኑ ከአህመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ በተነሳበት ቅፅበት መከስከሱን ቢቢሲ አስነብቧል።

በወቅቱ 12 የአውሮፕላኑን ሰራተኞች ጨምሮ 232 መንገደኞችን አሳፍሮ የነበረ ሲሆን፥ ከተነሳ በኋላ በ190 ሜትር ከፍታ ላይ ከአየር በረራ ተቆጣጣሪዎች ጋር የመጨረሻ ግንኙነት አድርጓል ተብሏል።

የአደጋው መንስኤ እስካሁን ያልተገለጸ ሲሆን፥ አውሮፕላኑ በመኖሪያ መንደር አካባቢ መከስከሱንም ነው ዘገባው ያመላከተው።

በህይወት ሰው ስለመትረፉ ምንም የተባለ ነገር የለም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ድርድር እስኪጠናቀቅ ድረስ የተኩስ አቁሙ መራዘሙን አስታወቁ

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በፓኪስታን ጥያቄ መሠረት ከኢራን ጋር የገቡትንየተኩስ...

ለኢትዮጵያ የግብርና ዘርፍ የሚውል የ40 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ ተፈቀደ

የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የልማት ክንፍ የሆነው ኢአይቢ ግሎባል (EIB...

ሃይንከን በአልኮል መጠኑ ጠንከር ያለ ቢራ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋወቀ

ሃይንከን ኢትዮጵያ በእለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ የሆነውን ዴሰፔራዶስ (Desperados)...