14 ሀገራት የተሳተፉበት 7ኛው ‘አግሮ ፉድ’ የንግድ ዓውደ ርዕይ በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ መካሄድ ጀመረ
በንግድ ዓውደ ርዕዩ ላይ ከ ቻይና፣ ጀርመን፣ ሕንድ፣ ሳዑዲ ዓረቢያ፣ ቱርክ እና የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶችን ጨምሮ 14 ሀገራት ተሳታፊ ሆነውበታል
ከሰኔ12 ጀምሮ እስከ ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ የሚካሄደውን ዓውደ ርዕይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴዔታ ሃሰን መሃመድ፣ በኢትዮጵያ የቱርክ አምባሳደር በርክ ባራን እና በኢትዮጵያ የብራዚል አምባሳደር ዣንዲር ፌሬራ ዶስ ሳንቶስ በይፋ አስጀምረውታል ።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴዔታ አቶ ሃሰን መሃመድ በአውደ ርአዩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት፥ ኢትዮጵያ የአግሮ ኢንዱስትሪ ዘርፉን ለማሳደግ ጠንካራ ስራዎችን እየሰራች መሆኑን ተናግረዋል
በተጨማሪም የአግሮ ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመገንባት ባለሃብቶች በአግሮ ኢንድስትሪው ዘርፍ ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል
ከየሀገራቱ ከ130 በላይ ድርጅቶች በዓውደ ርዕዩ ላይ የተሳተፉ ሲሆን የግብርና፣ የምግብና መጠጥ ግብዓቶች እና ፕላስቲክ፣ በዓውደ ርዕዩ ላይ ቀርበዋል።
