ቢቢሲ ‘ፀረ-ፍልስጤማዊ ዘረኝነት’ ያራምዳል የሚል ክስ ቀረበበት

Date:

107 የተቋሙ ሰራተኞች እና 300 የሚዲያ ኢንዱስትሪ ባለሙያዎች በጋራ በመሆን ለቢቢሲ አመራር ይፋዊ ደብዳቤ ፅፈዋል።

በደብዳቤውም ቢቢሲ የእስራኤል ጉዳይ ላይ ሲመጣ “ሳንሱር” እና “ለእስራኤል መንግስት እና ወታደራዊ አገልግሎት የህዝብ ግንኙነት ስራ በማከናወን ላይ ነው” በማለት ተቋሙ ላይ ክስ ሰንዝረዋል።

በዴድላይን የታተመው ደብዳቤው በተለይ የቢቢሲ የጋዛ ሜዲክስ ዶክመንተሪ ፊልም እንዳይሰራጭ መወሰኑን ተከትሎ ይህ የቅርብ ጊዜ ውሳኔ “በአጀንዳ ከተመሩ ውሳኔዎች ውስጥ አንዱ ነው” ብለዋል።

ሰራተኞቹ “አብዛኛው የቢቢሲ ሽፋን በፀረ-ፍልስጤም ዘረኝነት ይገለጻልም” ብለዋል።

በተጨማሪም ቢቢሲ የዩናይትድ ኪንግደም መንግስት በፍልስጤማውያን ላይ በሚደረገው ጦርነት የጦር መሳሪያ ሽያጮችን ወይም የህግ አንድምታዎቻቸውን ጨምሮ ምንም አይነት ጉልህ ትንታኔ አላቀረበም ብለዋል።

“የቢቢሲ ኤዲቶሪያል ውሳኔዎች ከእውነታው የራቁ ይመስላሉም ያሉ ሲሆን፤ ውሳኔዎች የተመልካቾችን ፍላጎት ከማገልገል ይልቅ የፖለቲካ አጀንዳን ለማሟላት የሚሰጡ ናቸው ብለን ለመደምደም ተገድደናልም” ብለዋል።

ደብዳቤውን የፈረሙት የቢቢሲ ሰራተኞች ስማቸው ይፋ ያልተደረገ ቢሆንም ጥሪያቸውን ከሚደግፉ የኢንዱስትሪው ሰዎች ግን ካሊድ አብደላ እና ሚርያም ማርጎልየስ ይገኙበታል ተብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...