የኤርትራዉ ቃል አቀባይ የማነ ገብረመስቀል ምን አሉ?

Date:

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገብረመስቀል፣ መቀመጫውን ዋሽንግተን ያደረገው “ዘ ሴንትሪ” የተሠኘው መንግሥታዊ ያልኾነ ተቋም በኤርትራ ላይ ያወጣው ሪፖርት “የስም ማጥፋት ውንጀላ” ነው በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሠፈሩት ጽሁፍ ውድቅ አድርገዋል።

የማነ፣ የተወሰኑ የተቋሙ የቦርድ አባላት፣ “በአደራዳሪነት ሽፋን የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጦርነትን በማባባስ” የሚታወቁ፣ ለኢትዮጵያ መንግሥት ወግነው የነበሩና የተመድ ጸጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ላይ ማዕቀብ እንዲጥል ከፍተኛ ሚና የተጫወቱ ነበሩ በማለት ወቅሰዋል።

ተቋሙ “ሥልጣና እ ዝርፊያ፤ የኤርትራ ጦር ጣልቃ ገብነት በትግራይ‘’ በሚል ርዕስ ከቀናት በፊት ባወጣው ሪፖርት፣ ኤርትራ ሠራዊቷን እንደገና እያስታጠቀችና ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦቿም በትግራይ በሰዎች ዝውውር፣ በሰዎች እገታና በሕገወጥ የወርቅ ማዕድን ንግድ እንደሚሳተፉ ገልጦ ነበር። [ዋዜማ]

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች...

በጋምቤላ ክልል በጀት ዓመት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ2 ቢሊዮን በላይ ጭማሪ አሳየ

 በጋምቤላ ክልል በበጀት አመቱ በተከናወነው የገቢ አሰባሰብ ዙሪያ የተሻለ...