“እስራኤል ከደቡባዊ ሊባኖስ እስክትወጣ ትጥቅ አንፈታም”

Date:

  • ሂዝቦላህ

ሂዝቦላህ፣ እስራኤል ከደቡባዊ ሊባኖስ እስክትወጣ ድረስ ትጥቅ እንደማይፈታ ማስታወቁን አልጀዚራ እና አል አረቢያ ዘግበዋል።

የሂዝቦላህ ዋና ፀሃፊ ነኢም ቃሲም ለአል አረቢያ እንደተናገሩት የአሜሪካ እና የእስራኤል ዛቻ ፓርቲያቸውን “እጅ እንዲሰጥ” ወይም የጦር መሳሪያ እንዲፈታ አይገፋፋውም።

ዋና ፀሃፊው በቴሌቭዥን ባደረጉት ንግግር “ይህ ማስፈራሪያ እጅ እንድንሰጥ አያደርገንም፤ በሊባኖስ እና በአካባቢው የሚደረገውን ወረራ ህጋዊ የማድረግ አካል አንሆንም” ብለዋል።

ዋና ፀሃፊው ሂዝቦላህ ለሰላም በሩ ክፍት መሆኑን ጠቅሰው፤ ነገር ግን ኢስራኤል የአየር ወረራዋን እስክታቆም እና ከደቡብ ሊባኖስ እስክትወጣ ድረስ ትጥቅ አንፈታም ብለዋል። እስራኤልን ከመጋፈጥም ወደኋላ አንልም ሲሉም ገልጸዋል።

ይህ ሁኔታ የቀጣናውን ውጥረት ሊያባብሰው ይችላል ተብሏል። ሂዝቦላህ እና እስራኤልም ወደ ከፍተኛ ግጭት ሊያመሩ እንደሚችሉ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...