በ3200 ካ•ሜ ስፋት ቦታ ላይ ያረፈው ባለ 4 ቤዝመንትና G±32 ቅይጥ አፓርትመንት “ኢዮር ታወር” በሚል ስያሜ ከግማሽ መንፈቅ በፊት ግንባታውን ማከናወን መጀመሩ ገልጿል።
የኢዮር ታወር ከወለል በታች ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ ከምድር እስከ 6ኛ ወለል የተለያዩ ለንግድና ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ የቢዝነስ ቦታዎች ከ7ኛ ወለል እስከ 31ኛ ወለል ድረስ ደግሞ ከባለ 1 እስከ ባለ 3 መኝታ ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን የያዘ መሆኑ ተጠቁሟል።
በሽያጭ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የፓልም ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ ሰላማዊት አያሌው የህንፃው ግንባታ ቁፋሮ ተጠናቆ የመሰረት ሙሌቱ በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የፓልም ሪል ስቴት ኢዮር ታወር ለየት ባለ መልኩ የኑሮ ደረጃን ለማሻሻል አላማ በማድረግ የጥራት ደረጃው ከፍ ባለ መልኩ እየተገነባ የሚገኝ እንደሆነ ነው የተገለፀው።
በሽያጭ ማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የፓልም ሪል ስቴት ብራንድ አምባሳደር አርቲስት አለማየሁ ታደሰን ጨምሮ በርካታ የድርጅቱ ደንበኞች ታድመዋል።
