በትራምፕ አስተዳደር የአሜሪካ የሕግ ፍልሰት ላይ እየተደረገ ያለው አጠቃላይ እርምጃ አካል በመሆኑ ለተማሪዎች፣ ለባህል ልውውጥ ተጓዦች እና ለመገናኛ ብዙኃን አባላት የሚሰጠው የቪዛ መስፈርት ጥብቅ ሊደረግ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል።
ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በጥር ወር ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ ስደተኞችን ለመግታት ሰፊ ዘመቻ ከፍተዋል።
ይህ የቅርብ ጊዜ እርምጃ በአሜሪካ የሚቆዩበትን ጊዜ ለማራዘም እንደገና ማመልከት የሚገባቸው ለዓለም አቀፍ ተማሪዎች፣ ለልውውጥ ሰራተኞች እና ለውጭ ጋዜጠኞች አዲስ እንቅፋት ይፈጥራል።
የቀረበው ሕግ ለዓለም አቀፍ ተማሪዎች ለሚሰጠው ኤፍ ቪዛ የተወሰነ የጊዜ ገደብ ያስቀምጣል።
የባህል ልውውጥ ተጓዦች እና የመገናኛ ብዙኃን አባላት በአሜሪካ እንዲሰሩ የሚፈቅደው J እና I ቪዛ በአሁኑ ጊዜ የሚሰጠው የፕሮግራሙን ወይም በዩናይትድ ስቴትስ የቅጥር ጊዜን መሰረት በማድረግ ነው።
የትራምፕ አስተዳደር ያቀረበው ሕግ እንደሚያመለክተው፣ ለውጡ በአሜሪካ የሚገኙ የቪዛ ባለቤቶችን “በተሻለ ለመከታተል” እንደሚያስፈልግ ይገልጻል።
በዓለም ዙሪያ ከ4,300 በላይ የትምህርት ተቋማት ዓለም አቀፍ አስተማሪዎችን የሚወክለው ናፍሳ የተባለው ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ትራምፕ አስተዳደር ይህን ውሳኔ እንዲሰርዝ ጠይቋል።
በነገራችን ላይ የትራምፕ አስተዳደር በሕጋዊ መንገድ ስደተኞችን መቆጣጠርን አጠናክሮ፣ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ሃሳብ በመቃወም የተማሪነት ቪዛዎቻቸውን እና ግሪን ካርዶቻቸውን የሰረዘ ሲሆን፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ስደተኞችን ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ ነጥቋል።
