ኢንፊኒክስ ኢትዮጵያ እና ተግባረ-ዕድ አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ

Date:

በትራንስሽን ማኑፋክቸሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማ ባለቤትነት የተያዘው ኢንፊኒክስ እና የአዲስ አበባ ተግባረ-ዕድ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ወጣቱን በቴክኖሎጂ ዘርፍ ለመደገፍ እና አብሮ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ጥቅምት 18/2018 አ.ም ተፈራርመዋል ።

የመግባቢያ ስምምነቱም የኢንፊኒክስኒ ክለብን በተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ  ኮሌጅ ለማቋቋም የሚያስችለው ነው ተብሏል።

በዚህም ተማሪዎቹ በግል እና ሙያዊ እድገት ላይ ያተኮሩ ወርክሾፖች እና የማማከር ፕሮግራሞች ውስጥ እንዲሳተፉ እድል እንደሚሰጥ ተገልጿል ።

እንዲሁም መምህራን የቴክኖሎጂ ስልጠና እንደሚያገኙ ተጠቅሷል።

ስለ ስምምነቱ አስፈላጊነት የገለፁት የአዲስ አበባ ተግባረ እድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ተሰፋዬ አድማሱ “ይህ የመግባቢያ ስምምነት ከጽሑፍ ሰነድ በላይ ነው ብለዋል።

የኮሌጁ ተማሪዎችም ከተግባራዊ ልምድ በተጨማሪ የስራ እድላቸውን እና በራስ መተማመናቸውን የሚያሳድጉበት መሆኑ ተጠቅሷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...