ይህ የተገለጸው ሆስፒታሉ የ25ተኛ አመት ክብረ በአሉን ባከበረበት ወቅት ነው።
ሆስፒታሉ ላለፉት 25 አመታት በሀገራችን የጤና ዘርፍ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ ማበርከት ሲሰራ መቆየቱም ተገልጿል።
በእለቱ ተክለሀይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል አርቲስት ቸርነት ፍቃዱን ብራድ አምባሳደር አድርጎ መሾሙ ተነግሯል
ተክለሃይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል በውስጥ ደዌ ፣ በሰሬጀሪ፣ በማህጸን እና ጽንስ ፣ በህጻናት እና ልጆች ህክምናም ፣ ከአንገት በላይ፣ በቆዳ እና አባላዘር ህክምና ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ እንደሚገኙበት ተጠቁሟል።
ሆስፒታሉ ዘመናዊ የሆኑ የህክምና መሳሪያዎች በመጠቀም ላለፋት አመታት እየሰራ ነበርም ተብሏል።
ሆስፒታሉ የምስረታ በዓሉን ከህዳር 14 እስከ ግንቦት 18 በተለያዩ በጎ አድራጎት ስራዎች፣ በነጻ ህክምና እንዲሁም በተመረጡ ቀናት ለሚወልዱ እናቶች ልዩ ሽልማትና ልዩ የህክምና ቅናሽ እንደሚኖርም ተገልጿል።
ተክለሃይማኖት በቀጣይ እየገነባ ያለው ኮምፕሬሄንሲቭ ሆስፒታል ሲጠናቀቅ ወደፊት 12 ቀዶ ህክምና ክፍሎች እና 200 አልጋዎችም እንደሚኖሩትም ይጠበቃል
ይህም ለተለያዩ ህመሞች ወደ ውጭ ሀገር ሄደው የሚታከሙ ሰዎችን ድካም በመቀነስ ለጤና ቱሪዝም የድርሻውን እንዲወጣ ያግዘዋል ተብሏል
