የኢትዮጵያ አየር መንገድ አመቺ ባልሆነ የአየር ፀባይ ምክንያት በረራዎች አቋረጠ

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባወጣው መግለጫ በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ጭጋጋማ እና ለበረራ አመቺ ያልሆነ የአየር ፀባይ አጋጥሞኛል ብሏል።

የተሰበሰበ የሚቲዎሮሎጂ መረጃ ይህ የአየር ፀባይ ለተወሰኑ ቀናት የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጧል ብሏል መግለጫው።

በዚህ ምክንያት ወደተወሰኑ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚደረጉ በረራዎችን ለማቋረጥ በመገደዱን ተናግሯል።

የአየር ፀባዩ እስከሚስተካከል እና በረራዎችን መቀጠል እስከሚቻል ድረስ መንገደኞች እንዲታገሱ ጠይቋል።

አስቸኳይ ጉዞ ያለባቸው መንገደኞችም ሌላ የጉዞ አማራጭ ይጠቀሙ ብሏል።

አየር መንገዱ በአየር ፀባይ ምክንያት የተስተጓጎሉ በረራዎች ወደ መደበኛ አገልግሎታቸው እንደተመለሱ ለመንገደኞች አሳውቃለው ብሏል በመግለጫው።

በዚህ ምክንያት ለሚፈጠሩ መጉላላቶችም ይቅርታ ጠይቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ጥቃት አድራሹ ከካሊፎርኒያ መሆኑን ትራፕ ገለፁ

ትናንት ቅዳሜ ምሽት በዋይት ሃውስ የጋዜጠኞች ማኅበር የእራት ግብዣ...

በኬንያ የመንገደኞች አውሮፕላን ከመስመሩ ወጥቶ ተከሰከሰ

ዛሬ ረፋድ ላይ በኬንያ ማንዴራ የአውሮፕላን ማረፊያ አንድ...

አቶ ጀማል አህመድ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ተጨማሪ 26 ሚሊየን ብር ሰጡ

አቶ ጀማል አህመድ ባሳለፍነው ወር ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ  ከሰጠው...

“የቻይና-አፍሪካ የምርምር ማዕከል”በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሊከፈት ነው

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና-አፍሪካ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር "የቻይና-አፍሪካ የምርምር...