ከመጠን በላይ መረጃ የመቀበል አደጋ

Date:

በአሁኑ የዲጂታል ዘመን በየቀኑ የምናስተናግደው የመረጃ ብዛት አዕምሯችን ሊሸከመው ከሚችለው በላይ እየሆነ መጥቷል። ይህ ሁኔታ በሳይንሱ “Cognitive Overload” ይባላል።

አዕምሯችን በአንድ ጊዜ ሊያከናውነው የሚችለው ተግባር ውስን በመሆኑ ተደራራቢ መረጃዎችን ስንጭንበት የሚፈጠር ችግር ነው።

መረጃዎች በበዙ ቁጥር ደግሞ አዕምሯችን በጥልቀት ማሰብ የሚችልበትን በቂ ትኩረት ያጣና በትንንሽና በማይረቡ መረጃዎች እንዲወጠር ይደረጋል። ይህ ደግሞ በዕለት ተዕለት ሥራችን ላይ ትኩረት እንድንነፈግና አዕምሯችን እንዲዝል በማድረግ ለከፍተኛ ድካም ይዳርገናል።

በተጨማሪም፥ መረጃ በበዛ ቁጥር ትክክለኛ ውሳኔ የመወሰን አቅማችን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስ ጥናቶች ያሳያሉ።

አዕምሯችን “Analysis Paralysis” በሚባለው ደረጃ ላይ ሲደርስ፣ ብዙ አማራጮችና መረጃዎች ስላሉት ብቻ ግራ ተጋብቶ ምንም ዓይነት ውሳኔ መወሰን ያቅተዋል።

በተለይ ደግሞ የምንቃወማቸው ሰዎች ወይም የማንደግፈው ሀሳብ ተደጋግሞ ሲቀርብልን፣ አዕምሯችን መረጃውን ከመተንተን ይልቅ ራሱን ወደ መከላከል ስሜት ስለሚያስገባ ለጭንቀትና ለውሳኔ ማጣት ይዳረጋል።

ይህ የአዕምሮ ውጥረት ( Cognitive Overload) የፈጠራ ችሎታችንን ከመግደሉም በላይ፣ አዕምሯችን በአንድ ነገር ላይ ሳይረጋ “ስታክ” ሆኖ እንዲቀር ያደርገዋል።

ብዙዎቻችን ረጅም ሰዓት በማይመለከተን ነገር ላይ የምናሳልፈውም አዕምሯችን መረጃን የመለየት አቅሙ ስለሚዝልና በቀላሉ በሚገኙ የ”ዶፓሚን” ሆርሞን አነቃቂዎች ስለሚታለል ነው።

ሰዓታችንን በማይመለከተን መረጃ ላይ የምናጠፋው አዕምሯችን በቂ መረጃ ስለሚያገኝ ሳይሆን፣ ጥራት ያለው መረጃ የመምረጥ አቅሙ ስለደከመ መሆኑን መረዳት ይገባል።

ስለዚህ የአእምሮ ጤናንና ሰላምን ለመጠበቅ፣ የሚመጣውን መረጃ ሁሉ ከመቀበል ይልቅ የሚጠቅመውን መምረጥ ግድ ይላህ።

በተጨማሪም አዕምሮ አረፍ ብሎ መረጃዎችን የሚያቀነባብርበት ጊዜ መስጠት ወሳኝ መሆኑን ሳይንሱ ይመክራል።

እናንተስ እንደዚህ አይነት ስሜት ውስጥ ገብታችሁ ታቃላችሁ ?

Source : BBC Worklife, Vocal

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...