ኢንፋንቲኖ የሩሲያን ዕገዳ የማንሳት ሃሳብ አላቸው

Date:

የዓለም አቀፉ እግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ በሩሲያ ላይ የተጣለውን ዕገዳ ሊያነሱ እንደሚችሉ አስታውቀዋል።

ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የገባችውን ጦርነት ተከትሎ ዩክሬንን “ወራለች” በሚል ብሔራዊ ቡድኗም ሆነ የእግር ኳስ ክለቦቿ ከማንኛውም ውድድር ከሦስት ዓመት በፊት መታገዳቸው ይታወሳል።

ኢንፋንቲኖም ይህ ዕገዳ “ያመጣው ለውጥ የለም” በሚል ለማንሳት ማሰባቸውን ይፋ አድርገዋል።

ዕገዳው “ጥላቻ ብቻ” ነው ያመጣው ያሉት ኢንፋንቲኖ እርምጃው ነገሮችን ሊያሻሽላቸው ይችላል የሚል ሃሳብ አላቸው።

የኢንፋንቲኖን አስተያየት ተከትሎ የዩክሬን ስፖርት ሚኒስትር ማትቪ ቢድኒ፥ ኢንፋንቲኖን “ሃላፊነት የጎደላቸው” በማለት ወርፈዋቸዋል።

ሚኒስትሩ “እግር ኳሱን ህፃናት ከሚገደሉበት እውነታ ጋር ሊለያዩት ሞክረዋል” ሲሉ የፕሬዚዳንቱን ሃሳብ ተችተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...