የዓለምን ሰላም ለማምጣት የታለመና አንድ ሚሊዮን ሕፃናትን ያሳተፈ የሜዲቴሽን መርሃ ግብር በታይላንድ

Date:

በዓለማችን እጅግ አስገራሚ ከተባሉ መንፈሳዊ ትዕይንቶች መካከል አንዱ በታይላንድ መከናወኑ ተገልጿል። ከአምስት ሺህ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ አንድ ሚሊዮን ሕፃናት በአንድነት በመሰብሰብ ለዓለም ሰላም የህሊና ጸጥታ ወይም ሜዲቴሽን ማድረጋቸው ተነግሯል።

ይህ መጠነ ሰፊ መርሃ ግብር “ሰላም የሚጀምረው ከውስጥ ነው” የሚለውን መርህ መሠረት ያደረገ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ ሕፃናቱ በጋራ በመሆን የሰላም፣ የፍቅር እና የረጋ መንፈስ ለዓለም እንዲሰራጭ አዎንታዊ ኃይልን እንደላኩም ተመላክቷል።

መርሃ ግብሩ ሕፃናቱ በዝምታ ውስጥ ሆነው አንድ ዓይነት ዓላማን በማንገብ፣ ሰላም በታላላቅ ፖለቲካዊ ውሳኔዎች ብቻ ሳይሆን በግለሰብ ደረጃ በሚደረግ የውስጥ ሰላም እንደሚመጣ ያስመሰከሩበት ነው ተብሏል።

ትንንሽ የሚመስሉ የሰላም እርምጃዎች እንደ ዝምታና ትንፋሽን የመቆጣጠር ልምምድ በዓለም ላይ ትልቅ ለውጥ የማምጣት አቅም እንዳላቸውም ትምህርት ተሰጥቶበታል።

ይህ ታላቅ ክስተት ሕፃናቱ ገና በለጋነታቸው ለዓለም ደህንነት እንዲያስቡና በውስጣቸው ሰላምን እንዲያሰርጹ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ታውቋል። በተጨማሪም መርሃ ግብሩ እያንዳንዱ ሰው ቆም ብሎ በማሰብና ለዓለም ሰላም በጎ ምኞትን በመመኘት የራሱን አሻራ ማሳረፍ እንደሚችል ትልቅ ማሳሰቢያ ሆኖ ማለፉ ታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን...