ሃሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል የሚያጭበረብሩ ግለሰቦች መኖራቸውን የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አስታወቀ

Date:


የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት እንዳስታወቀው አንዳንድ ህገወጦች በምስሉ ላይ የሚታየውን የአየር መንገድውክልና እና መሰል ሃሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል ህብረተሰቡን በማጭበርበር የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት እየሞከሩ መሆኑን ለተቋሙ በደረሰው ጥቆማ መረዳት መቻሉን አስታውቋል።

ተቋሙ እንዲህ አይነቱን የወንጀል ድርጊት እንደማይታገስ እና ተከታትሎ ለህግ እንደሚያቀርብ ያስታወቀ ሲሆን ህብረተሰቡም በእንደዚህ አይነት ሃሰተኛ ሰነድ እንዳይጭበረበርና መሰል አጠራጣሪ ሁኔታ ሲኖር ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ወንጀል ፈፃሚዎች በህግ ተጠያቂ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት የሚመነጩ የውክልና ሰነዶች ባር ኮድ ያላቸው ሲሆኑ ልዩ ውክልና ከሆነ ደግሞ የራሱ የሆነ መለያ ( security feature) እና ኤሌክትሮኒክስ/ደረቅ ማህተም የያዙ በመሆኑ በቀላሉ በሃሰተኛ መንገድ ሊዘጋጁ የማይችሉ መሆናቸውንም ተቋሙ አረጋግጧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...