የነዳጅ ዋጋ መቀነስና የገበያ መረጋጋት

Date:

በመካከለኛው ምሥራቅ ባለው ውጥረት ምክንያት ሰማይ ደርሶ የነበረው የነዳጅ ዋጋ፣ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጦርነቱ “በቅርቡ ይጠናቀቃል” የሚል ተስፋ ሰጪ ንግግር ማድረጋቸውን ተከትሎ ማክሰኞ ማለዳ ቅናሽ አሳይቷል።

በእስያ ገበያ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ በ8.5 በመቶ ቀንሶ በበርሜል 92 ዶላር ሲሸጥ፣ የአሜሪካው ግብይት ደግሞ የ9 በመቶ ቅናሽ በማሳየት በ88.60 ዶላር ተመዝግቧል።

ምንም እንኳን ዋጋው አሁንም ከጦርነቱ መነሻ ጋር ሲነፃፀር የ30 በመቶ ብልጫ ቢኖረውም፣ በትራምፕ ንግግር የታየው የገበያ መረጋጋት በእስያ አክሲዮን ገበያ ላይ መነቃቃትን ፈጥሯል።

በተለይም አብዛኛው ነዳጅ ከቀጣናው የሚገቡት የእስያ አገራት፣ በኢራንና በአሜሪካ መካከል ያለው ወታደራዊ ግጭት ጋብ ማለቱ ለኢኮኖሚያዊ ትንሳኤያቸው ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው ታምኖበታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...