ኢትዮጵያ እና ጀርመን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን 120ኛ ዓመት ያከብራሉ

Date:

በጀርመን የኢትዮጵያ አምባሳደር እስክንድር ይርጋ ከጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሰሃራ በታች አገራት እና ሳሄል ዳይሬክተር አምባሳደር ክርስቶፍ ሬትዝላፍ ጋር ዛሬ ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከርን ያለመ ነው።

ሀገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙታቸውን የጀመሩበት 120ኛ ዓመት በጋራ በሚያከብሩበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም በበርሊን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመለክታል።

ኢትዮጵያ እና ጀርመን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን የጀመሩት እ.አ.አ በ1905 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።

ሁለቱ ሀገራት በየሀገራቱ ኤምባሲያቸውን የከፈቱት እ.አ.አ በ1907 ነው።

ግብርና፣ ምግብ ዋስትና፣ ትምህርት፣ ማህበራዊ ዋስትና እና የግሉ ዘርፍ አቅም ግንባታ ከኢትዮ-ጀርመን የትብብር መስኮቹ መካከል ይጠቀሳሉ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...