የቻይና ባንክ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን በፋይናንስ ለመደገፍ ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የፋይናንስ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ የኢትዮጵያ ልዑክ፤ በአዲሱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የፋይናንስ ድጋፍ ዙሪያ ከቻይና ባንክ ጋር መነጋገሩን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ልዑኩ በውይይቱ ስለ ፕሮጀክቱ ቴክኒካዊ ንድፍ፣ የአፈጻጸም ጊዜ እና አጠቃላይ የፋይናንስ መዋቅር ማብራሪያ መስጠቱ ተጠቁሟል።

“ይህ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፍ ያላትን መሪነት የሚያጠናክር ከመሆኑም ባለፈ ለንግድ፣ ለቱሪዝም እና ለአጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ሚና ይጫወታል” ሲል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዑክ አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

የቻይና ባንክ በበኩሉ በፕሮጀክቱ ላይ ያለውን ከፍተኛ ፍላጎት በመግለጽ፤ የፋይናንስ መዋቅሩን ለመረዳት ከፕሮጀክቱ አስተባባሪ የአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ንቁ ግንኙነት መፍጠሩን አረጋግጧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የተላለፈ ጥሪ

በክልላችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እያደገ የመጣው የተሳሳተ ስሌት የወለደው...

በሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ ላይ በከባድ መሳሪያዎች የታገዘ  የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ

ለዓለም የንግድ ሰንሰለት እጅግ ስትራቴጂካዊ በሆነው የሆርሙዝ ባህረ ወሽመጥ...

የሲ.ኤን.ኤን መስራች ቴድ ተርነር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የዓለማችን ግዙፍ የዜና አውታር ሲኤንኤን መስራች ቴድ ተርነር በ87...

የኢትዮጵያ አጠቃላይ ብድር 51.8 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ይፋ ሆኗል

ኢትዮጵያ  በድጋፍ መልክ ከአሜሪካ በየዓመቱ  በመንግስት በኩል ፈሰስ የሚደረግ...