ስለ ፕላስቲክ ምርቶች

Date:

ኢትዮጵያ በቅርቡ ተግባራዊ ያደረገችውን የደረቅ ቆሻሻ አያያዝ እና አወጋገድ አዋጅ ተከትሎ፣ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የተከለከሉ የአንድ ጊዜ ብቻ አገልግለው ከሚጣሉ የፕላስቲክ ምርቶች መካከል በልዩ ሁኔታ መፈቀድ ያለባቸውን ለመለየት መረጃዎች እየተሰበሰቡ እንደሆነ የኢትዮጵያ አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ለአሐዱ አስታውቋል።

ባለስልጣኑ አዋጁን ለማስፈጸም የሚያግዝ መመሪያ በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝ የገለጹት የከተማ ቆሻሻ አያያዝና አወጋገድ ክትትል ዴስክ ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ዓለሙ፣ “ተቋማት በልዩ ሁኔታ እንዲፈቀዱላቸው የሚፈልጓቸውን የፕላስቲክ ምርቶች ለይተው እንዲያቀርቡ የጊዜ ገደብ ተሰጥቷቸዋል” ብለዋል።

በዚህ ሂደት በሱፐርማርኬቶችና በመገበያያ ስፍራዎች ሕብረተሰቡ እየተጠቀመባቸው የሚገኙ ምርቶች በአዋጁ አንቀጽ 14 ንዑስ አንቀጽ 6 ላይ በተቀመጠው ድንጋጌ መሠረት፣ ይህ ልዩ ሁኔታ የፕላስቲክ ከረጢቶችን እንደማይመለከት ተገልጿል።

የፕላስቲክ ከረጢቶችን በልዩ ሁኔታ ማስገባትም ሆነ መጠቀም በጥብቅ የተከለከለ ሲሆን፣ ለአንድ ጊዜ ብቻ ጥቅም ላይ የሚውሉ ምርቶች ላይ የሚወሰደው እርምጃ በአስተዳደራዊ ውሳኔ የሚቋጭ ቢሆንም የፕላስቲክ ከረጢቶችን ማምረት፣ መጠቀም፣ መሸጥ፣ ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት እና ማከማቸት የወንጀል ተጠያቂነት እንደሚያስከትል ኃላፊው አጽንኦት ሰጥተውበታል።

(አሐዱ ሬዲዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...

ከ 50 ሚሊዮን በላይ መራጮች በማንዋልና በዲጂታል ተመዝግበዋል

ከየካቲት 28_መጋቢት 28 የመራጮች ምዝገባ ሲካሄድ እንደነበር ይታወቃል። በተለያዩ ጉዳዮች...

በኦሮሚያ ክልል የ4.5 ሚሊዮን ዶላር የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ

ፈያ ኢንተግሬትድ ዴቬሎፕመንት ኦርጋናይዜሽን በኦሮሚያ ክልል የሚከሰቱ የበሽታ ወረርሽኞችን...