የጉምሩክ ኮሚሽን ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የኢኮኖሚ ውህደት ሚናዋን እንድትወጣ የበኩሉን ጥረት እያደረገ እንደሆነ ገለፀ

Date:



ይህ የተገለጸው ኢትዮጵያ እና ኬንያ የአንድ አለቅ የድንበር ጣቢያዎችን ለማስፋፋት የሚያስችል ውይይት ባካሄዱበት ወቅት ነው፡፡ ውይይቱ በጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ፣ በኢትዮጵያ የኬንያ አምባሳደር ጆርጅ አሪና፣ የዓለም ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ተወካዮች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መካከል እንደተደረገ የኢትዮጵያ ጉሙሩክ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ ከዓመታት በፊት አገልግሎት መስጠት የጀመረው የሞያሌ አንድ አለቅ የድንበር አገልግሎት ማዕከል ተደጋጋሚ ፍተሻዎችን በማስቀረት የተፋጠነ የጉምሩክ አገልግሎት እንዲኖር ማስቻሉን አንስተዋል፡፡

አክለውም ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ኢኮኖሚያዊ ውህደት ግንባር ቀደም ሚናዋን እንድትወጣ ኮሚሽኑ የበኩሉን ጥረት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ እና ኬንያ ተጨማሪ የጋራ አንድ አለቅ የድንበር አገልግሎት መስጫ ጣቢያዎችን ሱፍቱ እና ራሙ በሚባሉ የድንበር አካባቢዎች ለመገንባት ስለሚቻልበት ሁኔታም መክረዋል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...