ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ በጡረታ ከኃላፊነታቸው ተሰናበቱ

Date:

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንና የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ፣ የሊቀ ጳጳስነት ኃላፊነታቸውን በጡረታ ምክንያት ማስረከባቸው ተሰማ።

ብፁዕነታቸው ያቀረቡትን ከኃላፊነት የመነሳት ጥያቄ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዎ 14ኛ የተቀበሉት ሲሆን፣ ውሳኔው በቅድሥት መንበር ልዩ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ አማካይነት ይፋ ሆኗል።

በብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ምትክ የቀድሞው የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ረዳት ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ተስፋሥላሴ አዲሱ፣ የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተሹመዋል። ቤተክርስቲያኗ ባወጣችው ይፋዊ መግለጫ፣ አዲሱ ተሿሚ የአገረ ስብከቱን መንፈሳዊ አገልግሎት በበላይነት እንደሚመሩ ታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...