ሀገሪቱ ያሳለፈችው አዲስ መመሪያ ከ15 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች የራሳቸውን አካውንት መክፈት፣ ይዘቶችን መጫን፣ አስተያየት መስጠትም ሆነ በሕዝባዊ ግሩፖች ውስጥ መሳተፍን ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
ዕድሜያቸው 15 እና 16 የሆኑ ታዳጊዎች ማህበራዊ ሚዲያዎችን መጠቀም ቢችሉም፣ ጥብቅ የሆነ የይዘት ቁጥጥር እና የደህንነት ጥበቃ ይደረግባቸዋል።
ማህበራዊ ሚዲያ ኩባንያዎች አዲሱን ሕግ ተግባራዊ ለማድረግ እስከ 12 ወራት የሚደርስ ጊዜ ተሰጥቷቸዋል።
ይህ ውሳኔ ዩኤኢን እንዲህ ዓይነቱን ጥብቅ እገዳ በማስተዋወቅ የመጀመሪያዋ የአረብ ሀገር ያደርጋታል።
እርምጃው በታዳጊዎች ዲጂታል ደህንነት ዙሪያ የተወሰደ ትልቅ ምዕራፍ ተብሏል ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
