የኢትዮጵያ ሪድስ አምስተኛ ጉባኤ እየተካሄደ ነው

Date:

ለዓመታት የልጆች የንባብ ልምድ ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየሰራ የሚገኘው ኢትዮጵያ ሪድስ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው አምስተኛ ጉባኤው ከትላንት መጋቢት 24 ጀምሮ እየተካሄደ ይገኛል።

በዝግጅቱ ላይ ከተለያየ ዘርፍ የተወጣጡ ባለሙያዎች ስለ ልጆች ንባብ እና ተያያዥ ሀሳቦች ላይ መነሻ ጥናታዊ ፅሁፎች እያቀረቡ ሲሆን በፅሁፎቹም መነሻነት የሃሳብ ልውውጥ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህ ጉባኤ ላይ የልጆች ንባብ ባህልን ለማሳደግ አስተዋፅኦ ያደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች እውቅና የመስጠት መርሃግብር ይካሄዳል ተብሏል።

ኢትዮጵያ ሪድስ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ በሀገሪቱ በሁሉም ክልሎች ከ70 በላይ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ቤተመጽሐፍትን በማቋቋም ከመንግስት እና ከሌሎች አጋር ድርጅቶች ጋር አብሮ እየሰራም እንደሚገኝ አስታውቋል።

የ22 ዓመታት እድሜ ያስቆጠረው ኢትዮጵያ ሪድስ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች እና ልጆችን ባለፉት ዓመታት በንባብ አገልግሎት ተደራሽ ማድረጉን ገልጿል።

📸 ተክሌ ማርኮን

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አክሊሉ ወንድሞቹ ለንባብ በቃ

በፀሐፌ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተወልድ የልጅነት ታሪክ ላይ ያተኮረ ለታዳጊዎች...

የኢራን ተፈጥሮአዊ ምሽጎች እና ስትራቴጂካዊ ጥበብ

​ግዮን መጽሔት :- በመካከለኛው ምስራቅ የጂኦ-ፖለቲካ ትኩሳት...

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...