የእስራኤል የጸጥታ ካቢኔ ጋዛን ‘ለመያዝ’ እቅድ ማጽደቁን አንድ ባለሥልጣን ተናገሩ

Date:

የእስራኤል የጸጥታ ካቢኔ ያወጣው አዲስ እቅድ በሃማስ ላይ ወታደራዊ ጥቃት በማስፋፋት ጋዛን “መያዝ” ይጨምራል ሲሉ የእስራኤል ባለስልጣን መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የካቢኔው ምክር ቤት ሃማስን ለማጥፋት እና የተቀሩትን ታጋቾች ለመታደግ “ጠንካራ እርምጃ” ይወስዳል፡፡2.1 ሚሊዮን የጋዛ ህዝብንም “ከአደጋ ለመጠበቅ ይንቀሳቀሳል” ብለዋል።

ምን ያህል ግዛት በእስራኤል ወታደሮች እንደሚወሰድ ባይገልጽም “አይገቡም አይወጡም” ሲሉ አሳስበዋል።

ካቢኔው በመርህ ደረጃ ዕርዳታን በግል ኩባንያዎች ለማድረስ የተያዘውን እቅድ አጽድቆ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ የምግብ እጥረት አስከትሏል ያለውን የሁለት ወራት እገዳ ይቀርፋል ተብሏል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ሌሎች የእርዳታ ድርጅቶች ሃሳቡ መሰረታዊ የሰብአዊ መርሆችን መጣስ እንደሚሆን እና እንደማይተባበሩም ተናግረዋል።

የሃማስ ባለስልጣን የእስራኤልን “ግፊት እና ወሳኔ” ውድቅ አድርጓል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...