ለጤናው ዘርፍ “ከፍ ያለ” በጀት ለመመደብ ዝግጅቶች እየተደረጉ ነዉ

Date:

ለጤናው ዘርፍ በ2018 ዓ.ም. “ከፍ ያለ” በጀት ለመመደብ፤ “በቂ ዝግጅቶች” እየተደረጉ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ተናገሩ። የዘርፉን በጀት ከፍ ማድረግ ያስፈለገው አሁን ካለው “ወቅታዊ” እና “ነባራዊ” ሁኔታ አንጻር እንደሆነም ሚኒስትሯ ገልጸዋል። 

የጤና ሚኒስትሯ ይህን ያሉት ከብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት እና ዛሬ ሰኞ ግንቦት 4፤ 2017 በተላለፈው ቃለ ምልልሳቸው ነው። ዶ/ር በዚሁ ቃለ ምልልሳቸው፤ የጤና ዘርፉን በተመለከተ ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል። 

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለሚኒስትሯ ካቀረበው ጥያቄ አንዱ፤ የጤናው ዘርፍ የገንዘብ አቅምን የተመለከተ ነው። መንግስት ከሚመድበው በጀት በተጨማሪ ለጋሾች በሚሰጡት ገንዘብ በሚደገፈው በዚህ ዘርፍ፤ በአሁኑ ወቅት ስራዎች በምን መልኩ እየተሰሩ እንደሆነ እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ምን እንደሆኑ ለሚኒስትሯ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።  

ዶ/ር መቅደስ ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ በኢትዮጵያ ለጤናው ዘርፍ የሚመደበው በጀት ባለፉት ዓመታት እየጨመረ ቢመጣም፤ ከዓለም አቀፍ ስምምነቶች አንጻር ሲታይ መጠኑ “ዝቅተኛ” መሆኑን ተናግረዋል። ሚኒስትሯ ለዚህ በማጣቀሻነት ያነሱት፤ በቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) የመሪዎች ጉባኤ ላይ በሚያዝያ 1993 ዓ.ም. የጸደቀውን የአቡጃ ድንጋጌ ነው።

🔴 ለዝርዘሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/15860/

@EthiopiaInsiderNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በከተማዋ ከ24 ሺህ በላይ ንቁ የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ሳይቶች መኖራቸው ተገለፀ

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚደርሰውን የህይወትና የንብረት ጉዳት ለመቀነስ የቁጥጥርና የግንዛቤ...

አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ለሕክምና በወሰደችው መድኃኒት ምክንያት ከውድድር ታገደች

የቀድሞዋ የሁለት ጊዜ የዓለየቀድሞዋፒዮኗ ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ ከውድድር በፊት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ እውቅና ሊሰጣቸው ነዉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እውቅና የሚያገኙት የጎርጎርጎረሳዉያኑ 2026 በሞሮኮ...