የድምጻዊት ሐይማኖት ግርማ “ጅንኑ”የተሰኘው አራተኛ አልበም  ለአድማጭ ሊቀርብ ነው

Date:

ከዚህ በፊት ሶስት አልበሞች ለአድማጭ ያቀረበችው ኦማሔሬ በተሰኘው የሙዚቃ ስራ ከአድማጮቿ ጋር የተዋወቀችው ሐይማኖት ግርማ አራተኛ አልበሟ ለህዝብ ልታደርስ ቀን ቆርጣለች።

አዲሱ አራተኛ አልበሟ 12 ያህል ትራኮች እንደያዘ የተናገረችው ድምጻዊቷ በርካታ የሙዚቃ ሰዎች እንደተሳተፉበት ተናግራለች።

ድምጻዊቷ ሙዚቃ በግል ጉዳይ ምክንያት ላለፉት 12 አመታት አቁማ የነበረ ቢሆንም በጓደኞቿ ምክንያት ዳግም ወደ ሙዚቃው አለም በመምጣት አራተኛ አልበሟ ለመስራት በቅታለች።

ታምሩ አማረ ሚኪ ጃኖና ሌሎችም ስመጥር የሙዚቃው ሰዎች ተሳትፈውበታል ተብሏል።

አልበሙን ሰርቶ ለመጨረስ አንድ አመት ብቻ እንደወሰደባት የተናገረችው ሐይማኖት ግርማ በወጪም በኩል የተጋነነ ዋጋ አልተጠየኩበትም ብላለች።

አዲሱ አልበም ከበፊቶቹ አልበም እኩል እንዲደመጥ ጥራቱን ጠብቆ ተሰርቷል ነው የተባለው።

ሙዚቃውን ፕሮዲውስ ያደረገው ድምጻዊ ደሜ ሉላ አዲሱ የሐይማኖት ግርማ አልበም በናሆም ሪከርድስ በኩል ለአድማጭ ይቀርባል ብሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...