“የአፍሪካ ትምህርት ከቅኝ አገዛዝ ነፃ መውጣት አለበት”

Date:

በቅኝ ግዛት ተጽዕኖ ሥር ያለው የአፍሪካ የትምህርት ሥርዓት ከሀገር በቀል ዕውቀት ይልቅ ለምዕራባውያን ሞዴሎች ቅድሚያ ስለሚሰጥ ማኅበረሰቦች ችግሮቻቸውን በራሳቸው መንገድ እንዳይፈቱ አድርጓቸዋል ሲሉ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የልዩ ፍላጎት እና አካታች ትምህርት ክፍል ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አለማየሁ ተክለማርያም ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

📜 አክለውም ቋንቋ ለመረዳት እና ችግር ለመፍታት ቁልፍ በመሆኑ ህፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማር አለባቸው ብለዋል። እውነተኛ እውቀት የሚገኘው ከሀገር በቀል አስተሳሰብ እና ማኅበረሰብ ላይ በተመሠረተ ምርምር እንደሆነ የገለፁት ፕሮፌሰሩ፤ ይህም ወደ አካባቢያዊ ፈጠራ እና ቴክኖሎጂ ሊያመራ እንደሚችል አስረድተዋል።

“ኢትዮጵያ በወታደራዊ ኃይል በጭራሽ ቅኝ አልተገዛችም፤ ነገር ግን ባህላችን ቅኝ ተገዝቷል። ስለዚህ አስተሳሰባችንን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ማውጣት አለብን” ሲሉ ፕሮፌሰር ተክለማርያም ተናግረዋል።

📖 ፕሮፌሰሩ በቲክቶክ፣ ዩቲዩብ እና የውጭ ሚዲያዎች የተተኩት የአፍሪካ ባሕሎች እና የቃል ወጎች መነቃቃት እንደሚያስፈልጋቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል።

በሰው ሰራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ለአድዋ ድል መታሰቢያ በአሜሪካ ቀን ተሰየመ

በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት...

ኢሎን መስክ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊዮነር ሆነ

ኢሎን መስክ የሀብት መጠኑ 1 ትሪሊዮን ዶላር ያለፈ የመጀመሪያው...

የእግር ኳስ ዳኝነት በኢትዮጵያ

ገነነ መኩሪያ (ሊብሮ) ግዮን መጽሔት :- እግር ኳስ...

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...