ለኦሮሞ ምሁራን የኤርትራ ምላሽ

Date:

የኤርትራ መንግሥት ቃል አቀባይ የማነ ገ/መስቀል፣ 85 ያህል የኦሮሞ ምሁራን ሰሞኑን ለፕሬዝዳንት ኢሳያስ የጻፉት ግልጽ ደብዳቤ “በርካታ ስህተቶች” እና “መሠረት ቢስ ውንጀላዎች” ያሉበት ነው በማለት በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ዛሬ ምላሽ ሠጥተዋል።

አለመግባባቶችን ለመፍታት ትክክለኛው መንገድ፣ በደብዳቤው ጸሃፊዎችና በኤርትራዊያን አቻዎቻቸው መካከል “የፊት ለፊት ውይይት” ማድረግ እንደኾነም የማነ ገልጸዋል።

ፕሬዝዳንት ኢሳያስ በዘንድሮው የኤርትራ ነጻነት በዓል ላይ ስለ “ፖለቲካዊ ኦሮሙማ” ያነሱት ነጥብ፣ አንዳንድ “ወካይ ያልኾኑ” አካላት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚያራምዱትን አስተሳሰብ ብቻ የሚመለከት መኾኑንም የማነ አብራርተዋል።

የማነ አያይዘውም፣ ባኹኑ ወቅት በቀጠናው የጦርነት ነጋሪት እየጎሰሙ የሚገኙት “የኤርትራን ሉዓላዊ ግዛቶች በኃይል መያዝ የሚፈልጉ አካላት” እንጅ ኤርትራ አይደለችም ብለዋል።

የኦሮሞ ሕዝብ ለበርካታ ዓመታት ለመብቱ ሲያደርገው ለቆየው ትግል፣ ኤርትራ አጋርነቷን ስትገልጽ መቆየቷንም የማነ ገልጸዋል።

በውጭ የሚገኙ የኦሮሞ ብሄር ምሁራን፣ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ የኢትዮጵያ መንግሥትን ፖሊሲ ሲወቅሱ ኦሮሙማን በተሳሳተ አረዳድ አቅርበውታል በማለት፣ ባለፈው ሳምንት ለፕሬዝዳንቱ ግልጽ ደብዳቤ ጽፈው ነበር።

ዋዜማ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...