የታሪክ አፍታ

Date:

ልክ በዛሬዋ ቀን ሰኔ 5 1956ዓ.ም የፀረ አፓርታይድ ታጋዩ እና የደቡብ አፍሪካው የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ፓርቲ መሪው ኔልሰን ማዴላ የዕድሜ ልክ እስራት የተበየነባቸው ቀን ነበር፡፡

በአገር ክህደት ወንጀል እና በህገወጥ መንገድ ከአገር ለመውጣት በመሞከር በተደጋጋሚ በሮበን ደሴት እስር ቤት ሲታሰሩ ሲፈቱ የነበረ ሲሆን በኋላም አሻጥር ፈፅመዋል በሚል  ኔልሰን ማንዴላ የዕድሜ ልክ እስራት ተበየነባቸው።

ማንዴላ ጠባብ በሆነች ክፍል ያለማረፊያ ከከባድ የጉልበት ስራ ቅጣት ጋር ሲሰቃዩ ኖረው መጨረሻ ላይ አገራቸውን ከአፓርታይድ አገዛዝ ነፃ አውጥተው ፕሬዝዳንት እስከመሆንም ደርሰዋል፡፡

በዚህ ድርጊታቸውም የሰላም ኖቤል ተሸላሚ የሆኑ አፍሪካዊ መሪ ሆነው ነበር።

ማንዴላ በጥቂት ነጮች የበላይነት የተያዘውን የመንግስት እና የዘር መድሎን በመቃወም ከህጋዊ ሰላማዊ የፓርቲ ትግል እስከ የደፈጣ ትግል በማድረግ ያሰቡትን ዓላማ አሳክተዋል፡፡

የፀረ አፓርታይድ ታጋዩ እና የአፍሪካ ብሄራዊ ኮንግረስ ፓርቲ መሪው ኔልሰን ማዴላ በ95 አመታቸው እ.ኤ.አ በታህሳስ 5 2013 በደቡብ አፍሪካ አርፈዋል።

Nbc_Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...