ማክሮን ከሥልጣን የለቀቁትን ጠቅላይ ሚኒስትር መልሰው ሾሙ

Date:

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአራት ቀናት በፊት ሥልጣን የለቀቁትን ጠቅላይ ሚኒስትር ዳግመኛ ሾሙ።

የፈረንሳዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰባስሽን ሌኮርኑ አንድ ወር ሳይሞላቸው ሥልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል።

“ሥራውን አልፈልገውም፤ ኃላፊነቴን ጨርሻለሁ” ብለው ከሥልጣን የለቀቁት ሰባስሽን ሌኮርኑ ወደ ሥልጣን መመለሳቸው አነጋጋሪ ሆኗል።

በድጋሚ የተሾሙት ጠቅላይ ሚኒስትር እስከ ሰኞ ድረስ የቀጣዩን ዓመት በጀት ለፓርላማ ማቅረብ አለባቸው።

የ39 ዓመቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ከማክሮን ዋነኛ ደጋፊዎች አንዱ ናቸው።

በኤክስ ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት “ፕሬዝዳንቱ በሰጡኝ ኃላፊነት መሠረት የፈረንሳይን በጀት ከማቅረብ ባሻገር ፈረንሳውያን ለሚገጥሟቸው ችግሮች መፍትሔ አበጃለሁ” ብለዋል።

ባለፈው ሳምንት “ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኜ ለመቀጠል የሚያስችል ሁኔታ አልተሟላም” ሲሉ ለሥልጣናቸው መልቀቅ ምክንያት የሆናቸውን መግለጻቸው ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ምንገድ ላይ

(በእውቀቱ ስዩም) በቀደም ከሆነ ቦታ ተነስቼ ወደ አልሆነ ቦታ ስራመድ...

ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ በጡረታ ከኃላፊነታቸው ተሰናበቱ

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያንና የአዲስ አበባ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ...

አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ አዲስ መግለጫ አወጣች

ታዋቂዋ አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ለስፖርት ወዳጆችና ለደጋፊዎቿ ወቅታዊ መረጃ...