የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሃመድ፣ መንግሥታቸው እስራኤል ለሶማሌላንድ የሠጠችውን እውቅና ለመመከትና ሶማሌላንድን በተጨባጭ ከሶማሊያ ለመቀላቀል ወታደራዊ ኃይል ሊጠቀም እንደሚችል አስጠነቀቁ።
ፕሬዝዳንት ሞሃመድ፣ ሶማሊያ እስራኤል ለሶማሊላንድ በሠጠችው እውቅና “ብሄራዊ ደኅንነቷ አደጋ ላይ ከወደቀ ኃይል መጠቀም አንደኛው አማራጯ ይሆናል” በማለት ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ሞሃመድ፣ ሶማሊላንድ ከእስራኤል ላገኘችው እውቅና በምላሹ ለእስራኤል ወታደራዊ ጦር ሠፈር ለመስጠት እንደተስማማች ደርሠንበታል በማለት ከቀናት በፊት መናገራቸው አይዘነጋም።
