በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሲዳምኛ ቋንቋ መካተቱን ቦርዱ ገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ 2018 ዓ.ም ለሚያከናውነው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሲዳምኛ ቋንቋን ከመራጮች ምዝገባ እስከ ድምጽ አሰጣጥ ድረስ ባለው ሂደት ማካተቱን አስታውቋል።

አቶ መላከ አሉላ በቦርዱ የሎጀስቲክስ ክፍል ኃላፊ የምርጫ ቁሳቁስ እሸጋን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች በሰጡት ማብራሪያ ቦርዱ ከዚህ ቀደም በአምስት ቋንቋዎች የምርጫ ሥርዓቱ ሲከናወን እንደነበር አንስተዋል።

ከዚህ ቀደም የክልሉን (ሲዳማ) ሪፍረንደም ሲካሄድ እንዲሁም 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ የተካሄደው በአማርኛ ቋንቋ መሆኑን አቶ መላኩ  ገልጸዋል።

7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ቦርዱ የሲዳምኛ ቋንቋን በማካተት የምርጫ ሂደቱን በ6 ቋንቋዎች በማከናወን ላይ ይገኛል ተብሏል።

ቦርዱ ከዚህ ቀደም አማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ ፣ ትግረኛ፣ ሶማሊኛና አፋርኛ የምርጫ ሂደቱን ሲያከናውን እንደነበር ይታወሳል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...