በማንችስተር ደርቢ የኳታር የጸጥታ ሀይሎች ይሳተፋሉ

Date:

ዛሬ ምሽት 12:30 ላይ በታላቁ ኦልድ ትራፎርድ ስታዲየም በሚደረገው የማንቹሪያን ደርቢ ላይ የኳታር የጸጥታ ሀይሎች በደህንነት ስራ ላይ እንደሚሳተፉ ተነገሯል።

የማንቹሪያን ደርቢ ጨዋታ ተጠባቂ ሲሆን ባለሜዳዉ ማንችስተር ዩናይትድ ወደ ወራጅ ቀጠናዉ ዝቅ ላለማለት ለሲቲዝኖቹ ደግሞ የሻምፒዮንስ ሊግ መግቢያ ቦታ ለማግኘት የሚያደርጉት ጨዋታ ይሆናል።

ምንም እንኳ ማንችስተር ዩናይትድ ከታላላቅ ቡድኖች ጋር በሚያደርገዉ ጨዋታ ጠንካ መሆኑን ደጋግሞ ቢያሳይም ከነበረበት የከፍታ ደረጃ ከወረደ ግን አመታት ተቆጥረዋል። ዩናይትድ በማንቹሪያን ደርቢ የበላይነት የያዘዉ ቡድንም ነዉ።

በደርቢዉ ጨዋታ ላይ በማንችስተር ሲቲ በኩል ኤርሊንግ ሃላንድ በጉዳት የማይገኝ ሲሆን ዩናይትድ ማቲያስ ዲሊግትን እንደሚያጣዉ ተዘግቧል።

በጽጥታ ስራዉ ላይ ይሳተፋሉ ለተባሉት የኳታር የጸጥታ ሀይሎችም የማንችስተር ከተማ ፖሊስ ገለጻና መመሪያ ሰጥቷቸዋል።

 

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ሕገ መንግሥቱ መገንጠልን ይፈቅዳል ፤ ሕዝቡ ደግሞ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ዋጋ ይከፍላል”

አቶ ፍሬሕይወት ሳሙኤል(የ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ተቃርኖዎች›› መጽሐፍ ደራሲ) ግዮን መጽሔት :-...

ባለሙያ ባልሆኑ ግለሰቦች የሚሰራጭ የተዛባ መረጃ በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ነዉ

የሳይካትሪስት የሙያ ፈቃድና ሥልጠና የሌላቸው ግለሰቦች በተለያዩ መገናኛ...

የአውሮፓ ህብረት እና የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና የ1.2 ቢሊዮን ዩሮ ስምምነት ሊፈራረሙ ነው

በአውሮፓ ህብረት እና በኢትዮጵያ መካከል በሚካሄደው የንግድ ፎረም መክፈቻ...

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...